የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የዓሳ ምርታማነትን በሶስት ዕጥፍ ማሳደጉ ተገለፀ
19:31 19.08.2025 (የተሻሻለ: 19:34 19.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሌማት ትሩፋት መርሃ ግብር የዓሳ ምርታማነትን በሶስት ዕጥፍ ማሳደጉ ተገለፀ
በጥቅምት 2015 ዓ.ም በአርባ ምንጭ ከተማ በይፋ የተጀመረው ይህ ፕሮግራም የዓሣ ምርትን ከ255 ሺህ ቶን በላይ እንዳሳደገ፤ በግብርና ሚኒስቴር የዓሣ ሃብት ልማት ዴስክ ኃላፊ ፋሲል ዳዊት (ዶ/ር) ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
በቅርቡ ለምርቃት የሚበቃው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብም በቀን እስከ 14 ሺህ ኪሎ ግራም የዓሣ ምርት እያስገኘ እንደሚገኝም አስታውሰዋል፡፡
ከግድቡ ናይል ፐርች፣ ናይል ቴላፒ እና የመሳሰሉት ከፍተኛ ዋጋና ምርት ሰጪ ዝርያዎች እየተመርቱ ነው ተብሏል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X