ግጭት የቀጠለባት ኮንጎ ከኤም23 ጋር ለሚደረገው የሰላም ድርድር ቁርጠኝነቷን አረጋገጠች
20:27 18.08.2025 (የተሻሻለ: 20:34 18.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ግጭት የቀጠለባት ኮንጎ ከኤም23 ጋር ለሚደረገው የሰላም ድርድር ቁርጠኝነቷን አረጋገጠች
በኳታር አሸማጋይነት የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ማቀዷን ገልፃለች። ባለሥልጣናት “ዘላቂ ሰላም ለመመለስ እና የኮንጎን ሕዝብ ስቃይ ለማቅለል” ቁርጠኝነታቸውን አረጋግጠዋል።
የኳታር አማላጆች ረቂቅ ስምምነት እያሠራጩ እና ድርድሩም በቅርቡ ይካሄዳል ተብሎ ቢጠበቅም፤ በሰሜን እና በደቡብ ኪቩ ግጭቶች ቀጥለዋል። ኮንጎ ኤም23ን በአዲስ ጥቃት የከሰሰች ሲሆን ታጣቂዎቹ ደግሞ የመንግሥት ጥቃቶች ደርሶብናል ብለዋል።
በዋሽንግተኑ የሰኔ ስምምነትና የዶሃውን የሐምሌ መግለጫ ጨምሮ በቅርቡ የተደረጉ ስምምነቶች ትጥቅ ለማስፈታት፣ ታጣቂዎችን መልሶ ለማቋቋም እና የመንግሥትን ሥልጣን መመለስ የሚያስችል የድርጊት መርሃ-ግብር አስቀምጠዋል። ሆኖም ውጊያው የመጨረሻ የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ የሚደረገውን ጥረት ማስተጓጎሉን ቀጥሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X