ቦትስዋና እና አሜሪካ የቀረጥ ቅነሳን የተመለከተ ውይይት እያደረጉ ነው
18:04 16.08.2025 (የተሻሻለ: 18:14 16.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቦትስዋና እና አሜሪካ የቀረጥ ቅነሳን የተመለከተ ውይይት እያደረጉ ነው
ቦትስዋና ወደ ውጭ የሚምትልካቸውን ምርቶች የተጣሉትን ቀረጦች ቅነሳ እንዲደረግላት ለመቀነስ ወይም እንዲነሳላት ከአሜሪካ ጋር እየተወያየች መሆኑን መንግሥት በመግለጫው አስታውቋል፡፡
የንግድ እና የሥራ ፈጠራ ሚኒስቴር “እነዚህ ምክክሮች የሁለቱን ወገኖች ልዩ ስጋቶችን ለመፍታት እና የሁለትዮሽ የንግድ ግንኙነቶችን ለማጠናከር ያለሙ ናቸው” ብሏል፡፡
ሚኒስቴሩ፣ ውይይቶቹ በተለዋዋጭ የዓለም ንግድ ዐውድ ውስጥ የመጡ መሆናቸው እንዲሁም ከውይይቱ በኋላ ተጨማሪ ማስተካከያዎች ሊደረጉ እንደሚችሉ በመግለጽ ወቅታዊ መረጃዎችም እንደሚያቀርብ አክሏል፡፡
በቦትስዋና ሸቀጦች የተጣለው ቀረጥ በጎርጎሮሳውያኑ ሚያዝያ ወር ላይ ከተነገረው 37 በመቶ ቀንሶ፣ ከሳምንት በፊት በነሐሴ 7 ወደ 15 በመቶ ዝቅ ብሏል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ |