ናሚቢያ ከወባ እና ኮሌራ ነጻ መሆኗን በይፋ አወጀች
20:15 14.08.2025 (የተሻሻለ: 20:24 14.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ናሚቢያ ከወባ እና ኮሌራ ነጻ መሆኗን በይፋ አወጀች
አዲስ የወባ ወይም የኮሌራ በሽታ ከ28 ቀናት በላይ ሪፖርት አለመደረጉን ተከትሎ የወረርሽኝ ማብቃት ለማወጅ የሚያስችል መነሻ መሆኑን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስትር ኤስፔራንስ ሉቪንዳኦ አስታውቀዋል፡፡
በጎርጎሮሳውያኑ ታኅሣሥ 23 ቀን 2024 የጀመረው የወባ ወረርሽኝ መነሻው አንጎላ ነበር፡፡ 154 በበሽታው የሞቱ ሰዎችን ጨምሮ 95 ሺህ 412 ሰዎች የተያዙ ሲሆን ከእነሱ ውስጥ 17 ሺህ 164 ተያዦች ከውጭ የገቡ መሆናቸውን ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ “ያልተለመደ ከፍተኛ ጭማሪ” የታየበት እንደነበር ጠቁመዋል፡፡
ሉቪንዳኦ የጤና ሚኒስቴር በማኅበረሰቡ ውስጥ የወባ እና የኮሌራ መከላከል ሥራ አጠናክሮ እንደሚያስቀጥል ተናግረዋል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለጸገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X