ሱዳን የፀጥታው ምክር ቤት የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ትይዩ መንግሥት ማውገዙን አደነቀች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱሱዳን የፀጥታው ምክር ቤት የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ትይዩ መንግሥት ማውገዙን አደነቀች
ሱዳን የፀጥታው ምክር ቤት የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ትይዩ መንግሥት ማውገዙን አደነቀች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 14.08.2025
ሰብስክራይብ

ሱዳን የፀጥታው ምክር ቤት የፈጥኖ ደራሽ ኃይሉን ትይዩ መንግሥት ማውገዙን አደነቀች

ረቡዕ የፀጥታው ምክር ቤት የአማጺው የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል የትይዩ መንግሥት ምሥረታ፤ ለሱዳን አንድነትና የግዛት ሙሉነት ቀጥተኛ አደጋ መሆኑን በማወጅ ለሱዳን ሉዓላዊነት ያለውን ድጋፍ ዳግም አረጋግጧል፡፡

የፀጥታው ምክር ቤት የ2024ቱን 2736 የውሳኔ ሐሳብ በመምዘዝ ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በኤል ፋሼር ያደረገውን ከበባ እንዲያነሳ እና ያለተገደበ የሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት ተደራሽነት እንዲፈቀድ ጠይቋል፡፡

የሱዳን መንግሥት የሀገሪቱን ደህንነት፣ መረጋጋት እና ሉዓላዊነት ለማስጠበቅ እንዲሁም የሱዳን ሕዝብን ፍላጎት ለማገልገል ከዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጋር ለመተባበር ቁርጠኛ እንደሆነ አረጋግጧል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0