- Sputnik አፍሪካ, 1920
The Rising South
የዓለም አቀፍ የኃይል ሚዛን እየተቀየረ ባለበት በዚህ ወቅት - ኢትዮጵያን፣ አፍሪካን እና ሌሎችን የሚቀርጹ የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ እና የማህበራዊ ሃይሎች ወደምንመለከትበት ወደ “ራይዚንግ ሳዉዝ” እንኳን በደህና መጡ፡፡ ደቡባዊ አመለካከቶችን ወደ ዓለም አቀፋዊ ውይይት መድረክ ስናቀርብ የአሰላሳዮችን ፣ የመሪዎችን እና የለዉጥ ፈጣሪዎችን ሃሳብ ያድምጡ።

የአህያ ክሊኒክ፦ በአህዮች እና በባለቤቶቻቸው ህይወት ላይ ያመጣው ለውጥ

የአህያ ክሊኒክ፦ በአህዮች እና በባለቤቶቻቸው ህይወት ላይ ያመጣው ለውጥ
ሰብስክራይብ
“የአህዮች ዕድሜ ተሻሽሏል። ቀደም ሲል አንድ አህያ እስከ 10 ዓመት ይኖር ነበር፣ ነገር ግን አሁን እስከ 20 ዓመት ሊኖር ይችላል [...] በተጨማሪም የአህያ ባለቤቶችን በአጠቃላይ [የአህዮች] ደህንነታቸው፣ አመጋገባቸው፣ ማለትም የአመጋገብ ስርዓታቸው፣ የመኖሪያ ቤታቸው ሁኔታ ላይ እናስተምራለን።” ዶ/ር ደረጀ ፀጋዬ፣ የእንስሳት ሐኪም
በዚህ የራይዚንግ ሳውዝ ዝግጅት፣ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከአለም አቀፍ አጋሮች ጋር በመተባበር የሚያስተዳድራቸው የእንስሳት ህክምና ክሊኒኮች፣ የአህዮችን ደህንነት በማሻሻል እና በእነሱ ላይ ጥገኛ የሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ቤተሰቦች እንዴት እንደሚደግፉ እንቃኛለን።
የፕሮጀክቱ መሪ አቶ አለማየሁ ፋንታ፣ የእንስሳት ህክምና ባለሙያ ዶ/ር ደረጀ ፀጋዬ እና ከአካባቢው የአህያ ባለቤት አቶ ጥበበ ሰለሞን ጋር ስለ ክሊኒኩ ምስረታ እና ስላመጣው ለውጥ ውይይት አድርገናል፡፡
አዳዲስ ዜናዎች
0