በፑቲን-ትራምፕ ስብሰባ አሜሪካ የዩክሬንን ቀውስ ኃላፊነት ወደ አውሮፓ ኅብረት ሀገራት ታስተላልፋለች
18:46 11.08.2025 (የተሻሻለ: 18:54 11.08.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበፑቲን-ትራምፕ ስብሰባ አሜሪካ የዩክሬንን ቀውስ ኃላፊነት ወደ አውሮፓ ኅብረት ሀገራት ታስተላልፋለች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በፑቲን-ትራምፕ ስብሰባ አሜሪካ የዩክሬንን ቀውስ ኃላፊነት ወደ አውሮፓ ኅብረት ሀገራት ታስተላልፋለች
ይህም አውሮፓውያኑ የኔቶ አባል ሀገራት ከሩሲያ ጋር በቀጥታ እንዲደራደሩ ያስችላቸዋል ሲሉ የቀድሞ የቬትናም የሕዝብ ደህንነት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሥልጣን ንጉየን ሚን ታም ለስፑትኒክ ተናግረዋል።
አሜሪካውያን በድጋፍ ሰጪነት ሚና ብቻ እንደሚወሰኑም አስረድተዋል።
ታም አክለውም ሩሲያ “ዩክሬንን ከናዚ አስተሳሰብ ማላቀቅ"፣ “የጦር መሳሪያዎቿን ማስፈታት” እና የሀገሪቱን ገለልተኝነት በሚመለከት የያዘችውን ግብ ሳታሳካ ወደ ኋላ እንደማትመለስ ተናግረዋል።
🟠 የሩሲያ እና የአሜሪካ ፕሬዝዳንቶች በአላስካ በሚያደርጉት መጪው ስብሰባ ላይ በአሜሪካ የትኛውም ዓይነት ሀሳብ ቢቀርብ፤ በዩክሬን የሩሲያ የዘመቻ ግብ እንደማይቀየር ታም ገልፀዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X