በኬንያ በአውቶቡስ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 26 ከፍ ብሏል፤ የካውንቲው አስተዳዳሪ መንገዱ እንደገና እንዲሠራ ጠይቀዋል
18:35 10.08.2025 (የተሻሻለ: 18:44 10.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በኬንያ በአውቶቡስ አደጋ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 26 ከፍ ብሏል፤ የካውንቲው አስተዳዳሪ መንገዱ እንደገና እንዲሠራ ጠይቀዋል
የሀገሪቱ የጤና ሚኒስቴር በጽኑ ከቆሰሉት የአደጋው ሰለባዎች አንዱ በሆስፒታል ሕይወቱ እንዳለፈ እና ከአደጋው የተረፉ 26 ሰዎች አሁን ላይ የተረጋጋ ሁኔታ ላይ መሆናቸውንና አስቸኳይ ቀዶ ጥገናዎች እየተደረጉ እንደሆነ አክሏል።
▪ የኪሱሙ አስተዳዳሪ አንያንግ ንዮንግኦ ብሔራዊ የመንገዶች ባለሥልጣን አደጋው የደረሰበትን አደባባይ ብቻ ሳይሆን የመንገዱን አጠቃላይ መዋቅርም እንደገና ዲዛይን ሊያደርግ ይገባል ብለዋል።
በአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘገባ መሠረት፤ ሐዘንተኞችን የጫነ የትምህርት ቤት አውቶቡስ አደጋ በሚበዛበት አካባቢ ለመታጠፍ ሲሞክር ኪሱሙ ካውንቲ ውስጥ ቅዳሜ ተገልብጧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/