ከሁለት ሚሊየን በላይ ሰልፈኞች በትናንትናው ዕለት በኮትዲቯር ለተቃውሞ ወጡ
12:01 10.08.2025 (የተሻሻለ: 12:04 10.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ከሁለት ሚሊየን በላይ ሰልፈኞች በትናንትናው ዕለት በኮትዲቯር ለተቃውሞ ወጡ
ሰልፈኞቹ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎች ሎረንት ባግቦ እና ቲድጃን ቲያም በምርጫ ዝርዝሩ ውስጥ እንዲካተቱ ጠይቀዋል ሲሉ የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል፡፡
በተጨማሪም ፕሬዝዳንት አላሳን ኡታራ ለአራተኛ የሥልጣን ዘመን መወዳደራቸውን ተቃውመዋል፡፡
የወቅቱ የኮትዲቯር ሕገ-መንግሥት ለፕሬዝዳንቶች ገደብ የሌለው የአምስት ዓመት የሥልጣን ዘመን ሰጥቷል፡፡ ምርጫው በጥቅምት ወር እንደሚደረግም ታውቋል፡፡
ከማህበራዊ የትስስር ገፅ የተገኙ ምሥሎች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
© telegram sputnik_ethiopia

© telegram sputnik_ethiopia