ለታገደው የፍልስጤም የድጋፍ ቡድን ሰልፍ የወጡ 500 የሚጠጉ ሰዎች ለንደን ውስጥ መታሰራቸውን ፖሊስ አስታወቀ

ሰብስክራይብ

ለታገደው የፍልስጤም የድጋፍ ቡድን ሰልፍ የወጡ 500 የሚጠጉ ሰዎች ለንደን ውስጥ መታሰራቸውን ፖሊስ አስታወቀ

  ሰልፈኞቹ የፍልስጤም አክሽን ቡድን እንቅስቃሴ ላይ የተጣለውን እገዳ በመጣስ እና በመቋቋም የፖሊስ እና የፍትሕ ስርዓቱን አቅም ለመገዳደር ያለሙ ነበሩ።

ቡድኑ በጋዛ ውስጥ ከሚካሄደው ወታደራዊ ዘመቻ ጋር የተገናኙ ናቸው ያላቸውን ወታደራዊ አውሮፕላኖች ማውደምን ጨምሮ በፈጸማቸው ድርጊቶች ምክንያት በሐምሌ ወር በእንግሊዝ የሽብር ድርጅት ተብሎ ተፈርጇል።

የቡድኑ አባል መሆን ወይም ድጋፍ መስጠት እስከ 14 ዓመት በሚደርስ እስራት የሚያስቀጣ የወንጀል ድርጊት ነው።

ፖሊስ ለፍልስጤም አክሽን የድጋፍ መፈክር የያዘ ማንኛውንም ሰው በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተዘግቧል።

ከማህበራዊ የትስስር ገፆች የተገኙ ምሥሎች

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0