የጊኒ ቢሳው ፕሬዝዳንት ከሕዳሩ ምርጫ ዋዜማ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾሙ
16:31 08.08.2025 (የተሻሻለ: 16:34 08.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጊኒ ቢሳው ፕሬዝዳንት ከሕዳሩ ምርጫ ዋዜማ አዲስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሾሙ
ዑማሮ ሲሶኮ ኢምባሎ የቀደሞ ማዴም ጂ15 የተቃዋሚ ፓርቲ አስተባባሪ፤ ብራይማ ካማራን የፕሬዝዳንትነት ዘመናቸው ሦስተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል፡፡
ምርጫውን የተመለከቱ ዋና ዋና መረጃዎች፦
◻ የምርጫ ቀን፦ ቀደም ሲል ለሕዳር 21 ቀን ተቆርጦ የነበረው ፕሬዝዳንታዊና እና የእንደራሴዎች ምርጫ ወደ ሕዳር 14 ቀን 2018 ዓ.ም ተቀይሯል፡፡
◻ ሁለተኛ የሥልጣን ዘመን፦ ኢምባሎ የጊኒ ቢሳው ሕገ-መንግሥት በሚፈቅደው መሠረት ለሁለተኛ ጊዜ የሚወዳደሩ መሆኑን በማረጋገጥ መጋቢት ወር ላይ ሥልጣን ለመልቀቅ የገቡትን ቃል ከልሰዋል፡፡
◻ የሥልጣን ውሳኔ፦ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የኢምባሎ የሥልጣን ዘመን ነሐሴ 29 እንጂ ተቃዋሚዎች በጠየቁት የካቲት ወርላይ እንደማያበቃ አረጋግጧል፡፡
◻ የተቃዋሚዎች አቋም፦ ባለፉት ወራት ተቃዋሚዎች ኢምባሎ ሥርዓተ ሲመት ከፈፀሙበት ቀን ከአምስት ዓመት በኋላ ልክ የካቲት 20 ላይ የሥልጣን ዘመናቸው እንደተጠናቀቀ በመግለጽ ፕሬዝዳንት ሆነው መቆየታቸውን አይቀበሉም፡፡
ከጊኒ ቢሳው የፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት የተገኘ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X