አልጄሪያ በፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ፓስፖርት ያዢዎች ላይ እገዳ ጣለች
15:50 08.08.2025 (የተሻሻለ: 17:04 08.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አልጄሪያ በፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ፓስፖርት ያዢዎች ላይ እገዳ ጣለች
"ከአሁን ጀምሮ የፈረንሳይ ዲፕሎማሲያዊ ፓስፖርት ለሚይዙ ሰዎች የሚሰጡ ቪዛዎች፤ የፈረንሳይ ባለሥልጣናት በአልጄሪያውያን አቻዎቻቸው ላይ በሚጥሉት ተመሳሳይ ሁኔታዎች ላይ ተገዥ ይሆናሉ" ሲል የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በመግለጫው አስታውቋል፡፡
ስለዚህም በጎርጎሮሳውያኑ 2013 በአልጄሪያ እና በፈረንሳይ የዲፕሎማሲያዊ እንዲሁም መንግሥታዊ ፓስፖርቶች ለሚይዙ ሰዎች ይተገበር የነበረው የነፃ ቪዛ ስምምነት ተቋርጧል፡፡
የፈረንሳይ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የሁለቱን ሀገራት ውጥረት ተከትሎ መንግሥታቸው የአልጄሪያ ፖሊሲውን እንዲያጠብቅ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡ ማክሮን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራቸው ዣን-ኖኤል ባሮት የመንግሥታዊ እና የዲፕሎማሲ ፓስፖርት የያዙ ያለ ቪዛ ወደ ፈረንሳይ እንዲገቡ የሚፈቅደውን ስምምነት ማገዳቸውን ለአልጄሪያ እንዲያሳውቁ መመሪያ ሰጥተዋቸዋል፡፡
በሰው ሰራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X