የኢትዮጵያ የኢነተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 55 ሚሊየን እንደደረሠ ተገለጸ
13:12 08.08.2025 (የተሻሻለ: 13:14 08.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የኢነተርኔት ተጠቃሚዎች ቁጥር 55 ሚሊየን እንደደረሠ ተገለጸ
ቁጥሩ የኢትዮጵያ የዲጂታል ስትራቴጂ ከመጀመሩ በፊት 17 ሚሊየን እንደነበር የኢኖቬሽና እና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር አማካሪ አቢዮት ባዩ ገልፀዋል፡፡
25 ሚሊየን ኢትዮጵያውያን ለፋይዳ ብሔራዊ መታወቂያ እንደተመዘገቡም አክለዋል፡፡ በ5 ሚሊየን የኢትዮጵያ ኮደሮች ኢኒሼቲቭ 1.8 ሚሊየን ዜጎች እየተሳተፉ እንደሆነ እና 1 ሚሊየን የሚሆኑት የእውቅና ሠርትፍኬት እንደተሠጣቸውም ተገልጿል፡፡
ኢትዮጵያ በ2018 ዓ.ም ህዳር ወር ፊውቸር ቴክ ኤክስፖ 2025ን ታስተናግዳለች፡፡ ዝግጅቱ ስታርታፕችን ከኢንቨስተሮች ለማገናኘት እና የንግድ አጋርነቶችን ለመፍጠር እንደሚያግዝ ተነግሯል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X