ፑቲን በዩክሬን ቀውስ ዙሪያ ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጋር እንደተወያዩ ክሬምሊን አስታወቀ
21:21 07.08.2025 (የተሻሻለ: 21:24 07.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፑቲን በዩክሬን ቀውስ ዙሪያ ከደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ጋር እንደተወያዩ ክሬምሊን አስታወቀ
የሩሲያ ፕሬዝዳንት ትናንት ከዶናልድ ትራምፕ ልዩ መልዕክተኛ ስቲቨን ዊትኮፍ ጋር ያደረጉትን ውይይት ዐቢይ ውጤቶች ለሲሪል ራማፎሳ ገልፀዋል። የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ለመረጃው ምሥጋና አቅርበዋል።
ፑቲን ደቡብ አፍሪካ የምትገኝበትን የአፍሪካ መንግሥታት የሰላም ተነሳሽነት በደስታ እንደሚቀበሉም ገልፀዋል።
መሪዎቹ በሩሲያ እና ደቡብ አፍሪካ የስትራቴጂክ አጋርነቶች ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተወያይተዋል።
ግንኙነቱ እንዲቀጥልም ስምምነት ላይ ደርሰዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X