ጠፍቶ የነበረው የጋና ሄሊኮፕተር እንደተከሰከሰ እና ያሳፈራቸው ሚኒስትሮች ሕይወታቸው ማለፉ ተሠማ
18:38 06.08.2025 (የተሻሻለ: 18:44 06.08.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጠፍቶ የነበረው የጋና ሄሊኮፕተር እንደተከሰከሰ እና ያሳፈራቸው ሚኒስትሮች ሕይወታቸው ማለፉ ተሠማ
የጋና የጦር ኃይሎች ዚ-9 ሄሊኮፕተር፤ ረቡዕ ማለዳ ወደ ኦቡአሲ ሲጓዝ ከራዳር ጠፍቶ ነበር፡፡ አውሮፕላኑ አደጋው ሲያጋጥመው ሦስት የበረራ አባላት እና አምስት ተሳፋሪዎችን ጭኖ እንደነበር ታውቋል፡፡
የመከላከያ ሚኒስትር ኤድዋርድ ኦማኔ ቦአማህ እና የአካባቢ፣ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር ኢብራሂም ሙርታላ ሙሐመድ በአደጋው ሕይወታቸው አልፏል ተብለው ከሚገመቱ መካከል እንደሚገኙ በሚዲያዎች የተጠቀሱ የመንግሥት ቃል አቀባይ ተናግረዋል፡፡
ባለሥልጣናት የአደጋውን ምክንያት ለማጣራት ምርመራ የጀመሩ ሲሆን አደጋው ከደረሰበት ቦታ የተገኙ ምሥሎች የደረሰውን ውድመት ያሳያሉ፡፡
ከማኅበራዊ ሚዲያ የተገኙ ምሥሎች
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
