ግሎባል ፈንድ በኬንያ የሚመረተውን የኤችአይቪ መድኃኒት ለሞዛምቢክ አቀረበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱግሎባል ፈንድ በኬንያ የሚመረተውን የኤችአይቪ መድኃኒት ለሞዛምቢክ አቀረበ
ግሎባል ፈንድ በኬንያ የሚመረተውን የኤችአይቪ መድኃኒት ለሞዛምቢክ አቀረበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.08.2025
ሰብስክራይብ

ግሎባል ፈንድ በኬንያ የሚመረተውን የኤችአይቪ መድኃኒት ለሞዛምቢክ አቀረበ

ከሰሃራ በታች ያሉ የአፍሪካ ሀገራት በሀገር በቀል የኤችአይቪ መድኃኒቶች እና ምርመራዎች በጤና ዘርፍ ራሳቸውን የማስተዳደር አቅምን እያሳደጉ ነው ተብሏል፡፡ 

በመላው ዓለም የኤችአይቪ፣ የሳንባ ነቀርሳ እና የወባ በሽታዎችን ለመከላከል የገንዘብ ድጋፍ የሚያደርገው ግሎባል ፈንድ፤ በኬንያ የሚመረተውን ቲኤልዲ (የመጀመሪያ ተመራጭ የኤችአይቪ መድኃኒት) ለሞዛምቢክ አቅርቧል፡፡ አፍሪካ ሠራሹ ቲኤልዲ ወደ ፈንዱ አቅርቦት ሰንሰለት ውስጥ ሲገባ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡

የኬንያ ዩኒቨርሳል ኮርፖሬሽን በጎርጎሮሳውያኑ 2023 ለቲኤልዲ የዓለም ጤና ድርጅት ቅድመ-ምዘናን በማሟላት የመጀመሪያው የአፍሪካ አምራች ሆኗል፡፡

በዓለም ጤና ድርጅት የኤችአይቪ፣ “ሄፓታይተስ” እና የአባላዘር በሽታ በሽታዎች ፕሮግራሞች ዳይሬክተር ሜግ ዶኸርቲ፤ እርምጃው የአፍሪካን የመድኃኒት አቅርቦት ሰንሰለት የሚያጠናከር እና ያልተቋረጠ የኤችአይቪ ሕክምናን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0