የናይጄሪያ ነርሶች ከመንግሥት ጋር ባደረጉት ስምምነት ለአንድ ሳምንት የቆየውን አድማ በማስጠንቀቂያ አቆሙ
17:03 03.08.2025 (የተሻሻለ: 17:04 03.08.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየናይጄሪያ ነርሶች ከመንግሥት ጋር ባደረጉት ስምምነት ለአንድ ሳምንት የቆየውን አድማ በማስጠንቀቂያ አቆሙ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የናይጄሪያ ነርሶች ከመንግሥት ጋር ባደረጉት ስምምነት ለአንድ ሳምንት የቆየውን አድማ በማስጠንቀቂያ አቆሙ
መንግሥት የነርሶች ጥያቄ የሚመልስበትን ግዜ በግልፅ በማስቀመጥ ስምምነት ላይ መድረሱን የናይጄሪያ ነርሶች እና አዋላጆች ብሔራዊ ማህበር ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። ማህበሩ የስምምነቱን ትግበራ እንደሚከታተልም ጨምሮ አስታውቋል።
የነርሶቹ የሥራ አመፅ ሐምሌ 23 ሲጀመር በሰባት ቀናት ውስጥ ፍላጎታቸው ካልተሟላ ላልተወሰነ ጊዜ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉ አስጠንቅቀው ነበር።
ያቀረቡትን ጥያቄዎች፦
🟠 ከፍተኛ ክፍያ፣
🟠 የተሻሻለ የሥራ ሁኔታ መፍጠር፣
🟠 የሠራተኞች ብዛት መጨመር።
አርብ ዕለት የነርሶች ማህበር፤ ከጤና ጥበቃ ሚኒስትር አሊ ፓቴ እና የሠራተኛ ሚኒስትር መሀመድ ዲንግያዲን ጨምሮ ከመንግሥት ተወካዮች ጋር ተወያይተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X