የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የሀገሪቱ የእግር ኳስ ቡድን የቻን ዋንጫን ካነሳ 4.6 ሚሊዮን ዶላር ለመሸለም ቃል ገቡ
14:38 03.08.2025 (የተሻሻለ: 16:44 03.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኬንያ ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ የሀገሪቱ የእግር ኳስ ቡድን የቻን ዋንጫን ካነሳ 4.6 ሚሊዮን ዶላር ለመሸለም ቃል ገቡ
ፕሬዝዳንቱ በናይሮቢ የቁርስ መርሃ-ግብር ላይ ከቡድኑ አባላት ጋር ባደረጉት ስብሰባ ላይ “ይህ ለኬንያ በጣም ታሪካዊ ወቅት ነው፡፡ ኬንያ በእግር ኳስ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ቻንን [የአፍሪካ ሀገራት ሻምፒዮና] ስታስተናግድ ነው” ብለዋል።
ከዋናው ሽልማት በተጨማሪ ሩቶ በየደረጃው ማበረታቻዎችን ቃል ገብተዋል፦
⏺ ለሩብ ፍፃሜ 464,500 ዶላር፣
⏺ ለግማሽ ፍፃሜ 542,000 ዶላር፣
⏺ ነሐሴ 24 ለሚደረገው የውድድሩ የፍጻሜ ጨዋታ ከ697,000 ዳላር በላይ።
አንድ ጨዋታ ባሸነፉ ቁጥር እያንዳንዱ ተጫዋች ከ7,741 ዶላር በላይ የሚያገኝ ሲሆን ለአቻ ውጤት ደግሞ ግማሹ ይደረሳቸዋል።
ኬንያ፣ ኡጋንዳ እና ታንዛኒያ በጋራ የሚዘጋጁት ለአንድ ወር የሚቆየው ውድድር ቅዳሜ በዳሬሰላም፣ ታንዛኒያ ተጀምሯል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
