በሁሉም ዘመናት በምዕራባውያን የተዘረፉት የምሥራቃውያን ውድ ቅርሶች
17:44 02.08.2025 (የተሻሻለ: 17:54 02.08.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሁሉም ዘመናት በምዕራባውያን የተዘረፉት የምሥራቃውያን ውድ ቅርሶች
በኢራቅ እንግሊዛውያኑ ያነጣጠሩባት የመጀመሪያዋ ዒላማ በኦውስተን ሄንሪ ሌያርድ የተገኘችው ነነዌ ከተማ ነበረች። እሳቸው "አርኪኦሎጂስት ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ ወኪልም ነበሩ" ሲሉ የጥንታውያን ቅርሶች እና የሙዚዬሞች ባለሙያ ካውታር መሐመድ ለስፑትኒክ ተናግረዋል፡፡
የሶሪያ ጥንታዊቷ ከተማ ፓልሚራ በእንግሊዛውያን እና በፈረንሳያውያን ባለሀብቶች ሰለባ ሆናለች፡፡
በአሜሪካ ወረራ የኢራቅ ብሔራዊ ሙዚዬምን ጨምሮ ወደ 50 በሚጠጉ የአርኪኦሎጂ ቦታዎች፣ 16 ሺህ ገደማ ቅርሶች ተዘርፈው በሕገ-ወጥ መንገድ ወደ ውጭ ሀገር መዘዋወራቸውን ባለሙያው ያስታውሳሉ።
የቅርቡ የሶሪያ የእርስ በርስ ጦርነት ደግሞ ለዓለም አቀፍ የሕገ-ወጥ ዝውውር መረቦች ምቹ መደላደል ፈጥሯል።
የእነዚህ ጥንታዊ ቅርሶች መዳረሻ የት ነው? ካውታር መሐመድ ሦስት ዐቢይ መዳረሻዎችን ለይተዋል፦
◾በለንደኑ ብሪቲሽ ሙዚዬም
◾በኦክስፎርድ የሚገኘው አሽሞሊያን ሙዚዬም
◾በጨረታ ቤቶች እና በግለሰቦች አጅ
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X