ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ
16:34 31.07.2025 (የተሻሻለ: 16:54 31.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ
የኢትዮጵያ እና የጂቡቲ መከላከያ ኮሚቴ አብረው በሚሠሯቸው የሠላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
ውይይት የተደረገባቸው የስምምነቱ ጉዳዮች፦
የፀጥታና ደህንነት መረጃ ልውውጥ፣
ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን መግታት፣
ሽብርተኝነትን መከላከል፡፡
የመከላከያ ውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክቶሬት ሜጄር ጄነራል ተሾመ ገመቹ፤ “በዚህ ቀጣና አብሮ እንደሚኖር ወዳጅ ሀገር፤ የጋራ ተጠቃሚነታችንን በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ በትብብር መሥራታችን በአካባቢው ያለውን ተግዳሮት አሸንፎ ለመውጣት የማይተካ ሚና አለው” ብለዋል።
በአዲስ አበባ ስምምነቱን የፈረሙት የጂቡቲ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም አማካሪ ኮሎኔል ማጆር አብዱረህማን አብዲ፤ ሁለቱ ሀገራት ያደረጉት ስምምነት ለቀጣናው የሚኖረው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

1/2
© telegram sputnik_ethiopia

2/2
© telegram sputnik_ethiopia
1/2
© telegram sputnik_ethiopia
2/2
© telegram sputnik_ethiopia