ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ
ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 31.07.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ

የኢትዮጵያ እና የጂቡቲ መከላከያ ኮሚቴ አብረው በሚሠሯቸው የሠላምና ደህንነት ጉዳዮች ላይ መስማማታቸውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ውይይት የተደረገባቸው የስምምነቱ ጉዳዮች፦

የፀጥታና ደህንነት መረጃ ልውውጥ፣

ሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውርን መግታት፣

ሽብርተኝነትን መከላከል፡፡

የመከላከያ ውጭ ግንኙነትና ወታደራዊ ትብብር ዋና ዳይሬክቶሬት ሜጄር ጄነራል ተሾመ ገመቹ፤ “በዚህ ቀጣና አብሮ እንደሚኖር ወዳጅ ሀገር፤ የጋራ ተጠቃሚነታችንን በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ በትብብር መሥራታችን በአካባቢው ያለውን ተግዳሮት አሸንፎ ለመውጣት የማይተካ ሚና አለው” ብለዋል።

በአዲስ አበባ ስምምነቱን የፈረሙት የጂቡቲ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም አማካሪ ኮሎኔል ማጆር አብዱረህማን አብዲ፤ ሁለቱ ሀገራት ያደረጉት ስምምነት ለቀጣናው የሚኖረው ፋይዳ የጎላ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ኢትዮጵያ እና ጂቡቲ በፀጥታና ደህንነት ዙሪያ ስምምነት ተፈራረሙ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0