ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ
ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 30.07.2025
ሰብስክራይብ

ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክና በግብርና ሚኒስቴር በጋራ የተነደፈው ይህ ውጥን፤ ከሀገሪቱ የኢኮኖሚ ማሻሻያ፣ የአሥር ዓመት የልማት ዕቅድና ብሔራዊ የግብርና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ጋር የተጣጣመ ነው።

"ይህ ተነሳሽነት የፋይናንስ ተቋማት በገጠር ትራንስፎርሜሽን ውስጥ እንደ ስትራቴጂካዊ አጋር እንዲሳተፉ መድረክ ይፈጥራል፡፡ እንደ አበዳሪ ብቻ ሳይሆን ሁሉን አቀፍ እድገት ለማስፈንም ይሠራሉ" ሲሉ የግብርና ሚኒስትር ግርማ አመንቴ በማስጀመሪያ መርሃ-ግብሩ ላይ ተናግረዋል፡፡

የብሔራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ በበኩላቸው የፍኖተ ካርታው ትግበራ በግብርና ሚኒስቴር በበላይነት በሚቆጣጠረው አስተባባሪ ኮሚቴ እና እቅዱን በውጤታማነት ለማስፈጸም በተቋቋመው የቴክኒክ ኮሚቴ ድጋፍ እንደሚመራ አመልክተዋል።

ሀገራዊ ስትራቴጂው አርሶና አርብቶ አደሮች የባንክ አገልግሎትን ለማግኘት የሚያጋጥሟቸውን ከፍተኛ ወጪና የጊዜ መጓተት ለመፍታት ያለመ ነው።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
ብሔራዊ የግብርና ፋይናንስ ትግበራ ፍኖተ ካርታ ይፋ ሆነ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0