ናይጄሪያ ለኢትዮጵያ 2 ሺህ የካሽው ችግኝ እና 100 ሺህ ዘር በሥጦታ አበረከተች
11:22 28.07.2025 (የተሻሻለ: 11:24 28.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ ለኢትዮጵያ 2 ሺህ የካሽው ችግኝ እና 100 ሺህ ዘር በሥጦታ አበረከተች
የናይጄሪያ ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ ይዘው የመጡትንና 600 ሄክታር የሚጠጋ መሬት ያለማል የተባለውን ልገሳ፤ የኢትዮጵያ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ኢፋ ሙለታ ተረክበዋል፡፡ ይህም ሀገራቱ በአፍሪካ ዘላቂ የግብርና ልማት ለማረጋገጥ የጀመሩት የጋራ ቁርጠኝነት አካል ነው ተብሏል፡፡
ኢትዮጵያ ሰኔ 2025፣ 2 ሺህ የሐስ አቮካዶ ችግኝ እና 2 ሺህ የቡና ችግኝ ለናይጄሪያ መለገሷን ተከትሎ የመጣ መሆኑን የናይጄሪያ ሚዲያ ዘግቧል።
ምክትል ፕሬዝዳንት ካሺም ሼቲማ በአዲስ አበባ እየተካሄደ በሚገኘው ሁለተኛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የምግብ ሥርዓት ጉባኤ ናይጄሪያን ወክለው እየተሳተፉ ይገኛሉ፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X