ሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ቫልዳይ ጉባኤ ሊጀምር ነው
10:34 28.07.2025 (የተሻሻለ: 10:44 28.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሦስተኛው የሩሲያ-አፍሪካ ቫልዳይ ጉባኤ ሊጀምር ነው
ጉባኤው “በተከፋፈለችው ዓለም እውነተኛ ፖለቲካ፤ በሩሲያ እና በደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለውን ግንኙነት ዳግም ማጤን” በሚል መሪ ቃል፣ ከሚከተሉት ሀገራት የተውጣጡ ባለሙያዎችን እና የፖለቲካ ሰዎችን ያሰባስባል፦
ኮትዲቯር፣
ግብጽ፣
ዚምባቡዌ፣
ሩሲያ፣
ደቡብ አፍሪካ፣
ታናዛኒያ፡፡
የጉባኤው ግቦች የሚከተሉትን ያካትተታሉ፦
🟠 የሩሲያ አፍሪካ ባለሙያዎች ትሥሥርን መገንባት እና ማጠናከር፣
🟠 በቁልፍ ዓለም አቀፍ ፈተናዎች ላይ ምስጢራዊ ውይይቶችን ማድረግ፣
🟠 ለውጭ ፖሊሲ ባለሙያዎች ገቢራዊ የሚሆኑ የፖሊሲ ምክሮችን ማዘጋጀት፡፡
በፕሪቶሪያ የሚካሄደው የአንድ ቀን የሩሲያ-አፍሪካ ቫልዳይ ጉባኤ የመክፈቻ እና አራት የጭብጥ ውይይቶች አሉት፡፡
ውይይቶቹ፦
🟠 ቡድን20 እና ብሪክስ፤ በተለዋዋጩ የዓለም አሰላለፍ ውስጥ ያላቸው ሚና፣
🟠 በሩሲያ፣ በደቡባዊ አፍሪካ ሀገራት እና በመላው አፍሪካ ሀገራት መካከል ያለው ሰብዓዊ ትብብር እና የታሪካዊ ትውስታዎች ሚና፣
🟠 የሩሲያ እና የደቡብ አፍሪካ የሁለትዮሽ ግኑኝነት፣
🟠 ትራምፕ እና የዓለም አሰላለፍ፡፡
የስፑትኒክ አፍ ሪካ ጋዜጠና በቦታው ይገኛል! ይከታተሉን
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X