የቀድሞ የፈረንሳይ የደህንነት ወኪል በአፍሪካ የህፃናት መደፈር ወንጀሎችን በማመቻቸት ታሰረ
17:12 27.07.2025 (የተሻሻለ: 17:14 27.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የቀድሞ የፈረንሳይ የደህንነት ወኪል በአፍሪካ የህፃናት መደፈር ወንጀሎችን በማመቻቸት ታሰረ
የ58 ዓመቱ የቀድሞ ወታደር ሰኞ በቁጥጥር ስር ውሎ አርብ ታስሯል።
የሚከተሉት ክሶች ተመስርተውበታል፦
🟠 ከባድ የሰዎች ዝውውር ወንጀል፣
🟠 የህፃናት አስገድዶ መድፈር እና ወሲባዊ ጥቃት፣
🟠 የህፃናት ወሲባዊ ምስሎችን መያዝ።
ተጠርጣሪው በዋናነት በኬንያ የህፃናት ወሲባዊ ትንኮሳን በመምራት እና በመክፈል እንዲሁም እነዚህን ድርጊቶች ለራሱ እርካታ በመቅረጽ ተከሷል።
ወንጀሎቹ የተጋለጡት የህፃናት ወሲባዊ ወንጀሎችን መዋጋት ላይ ትኩረቱን ያደረገው የአሜሪካ ፋውንዴሽን ቪዲዮዎቹን በበየነ መረብ ላይ ማግኘቱን ተከትሎ ለፈረንሳይ ፖሊስ ካሳወቀ በኋላ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X