የሩሲያ ገዥ ፓርቲ ከአፍሪካ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ ገዥ ፓርቲ ከአፍሪካ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል
የሩሲያ ገዥ ፓርቲ ከአፍሪካ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል - Sputnik አፍሪካ, 1920, 26.07.2025
ሰብስክራይብ

የሩሲያ ገዥ ፓርቲ ከአፍሪካ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር ያለውን ትብብር ለማጠናከር ከፍተኛ ትኩረት ይሰጣል

በደቡብ አፍሪካ የቀድሞ የነጻነት ንቅናቄዎች ስብሰባ ላይ የተሳተፉ ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች የዩናይትድ ሩሲያ የፖለቲካ ፓርቲ የረጅም ጊዜ አጋሮች መሆናቸውን፤ የፓርቲው ሊቀመንበር ዲሚትሪ ሜድቬዴቭ ለተሳታፊዎች እና እንግዶች ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ላይ ገልጸዋል።

ከእነዚህ ፓርቲዎች ጋር በትብብር ለመሥራት ስምምነቶች እንዲሁም "ለሀገራት ነጻነት" የተሰኘው ዓለም አቀፍ ፀረ-አዲሱ ቅኝ አገዛዝ ንቅናቄ የጋራ ተነሳሽነቶች እየተተገበሩ መሆኑንም አክለዋል።

ዩናይትድ ሩሲያ ከአፍሪካ የፖለቲካ ኃይሎች ጋር የሚደረገውን ትብብር ከፍ አድርጎ ይመለከታል ያሉት ሜድቬዴቭ፤ ስብሰባውን ለነጻነት እና ለሉዓላዊነት በሚደረገው ትግል ቁልፍ እርምጃ አድርጎ እንደሚቆጥረው ተናግረዋል።

የአፍሪካ አጋሮች በበኩላቸው ነፃ ልማታቸውን የማስጠበቅ መብታቸውን ለመከላከል ዩናይትድ ሩሲያ የሚያደርገውን ድጋፍ እንደሚያደንቁ እና ፓርቲው እንደዚህ አይነት ተነሳሽነቶችን በመደገፍ እውነተኛ ባለብዙ ዋልታ ዓለም ለመፍጠር አስተዋጽኦ ማድረጉን እንደሚቀጥልም አስረግጠዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0