ኒጀር የገዢው ፓርቲ የምስረታ በዓልን አከበረች

ኒጀር የገዢው ፓርቲ የምስረታ በዓልን አከበረች
በኒጀር የሀገር አድን ብሔራዊ ምክር ቤት (ሲኤንኤስፒ) ሥልጣን በያዘበት ሁለተኛ ዓመት የምስረታ በዓል ላይ ጄኔራል ትቺያኒ ባደረጉት ንግግር፤ የኒጀር ሕዝብ ወደ ነፃነት የሚወስደውን "አስቸጋሪ መንገድ" የገነባበትን "ቁርጠኝነት እና ድፍረት" አሞካሽተዋል።
ትቺያኒ ላለፉት ሁለት ዓመታት "ኒጀርን የማስገዛት ጎታች ስርዓት" ተለቆብናል ብለዋል። የውጭ ኃይሎች ሀገሪቱን በእገዳ፣ በጦርነት ማስፈራራት፣ በሽብር፣ በማጭበርበርና የተሳሳተ መረጃ በማሰራጨት ዘመቻዎች ለማተራመስ እንደሞከሩ ወንጅለው፤ በኒጀር ሕዝብ "ዕለታዊ ሕይወት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ" እንዳሳደሩ ጠቅሰዋል።
ፕሬዝዳንቱ ለኒጀር ሁለት የተለያዩ መንገዶችን አቅርበዋል፦
🟠 እንዳለፈው ፖለቲካ እና ለፈረንሳይ ፈቃድ በመገዛት ወደ "ታቀደ ትርምስ" እና ዘላቂ ባርነት ማምራት፣
🟠 ወይም ባርነትን አሻፈረኝ በማለት እና "የኒጀርን ጥቅም ያለ ምንም ብዥታ ወይም ቸልተኝነት መጠበቅ።
ትቺያኒ ኒጀር ለሉዓላዊነቷ ያላትን የማይናወጥ ቁርጠኝነት አረጋግጠዋል።
ፕሬዚዳንቱ የመከላከያ እና የፀጥታ ኃይሎች ላደረጉት መስዋዕትነት እና ሙያዊ ብቃት፣ በታላቁ የመስኖ ፕሮግራም ውስጥ ለተሳተፉት፣ ለታታሪው ኒጀር ሕዝብ ቁርጠኝነት እና ለሀገሪቱ ወዳጆች ምስጋና አቅርበዋል።
ኒጀር በትክክለኛው መንገድ ላይ ትገኛለች ያሉት ትችያኒ፤ ምንም አይነት መሰናከል ለሀገሪቱ ያላቸውን ቁርጠኝነት ሊያዳክም ወይም የጋራ ፕሮጀክታቸውን እንዳያሳኩ ሊያግድ እንደማይችል ገልጸዋል። ትቺያኒ የሀገሪቱ ህልውና እና የወደፊት ዕጣ ፈንታ አደጋ ላይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X