ከሊቢያ ጋር በባሕር ድንበር ዙርያ ውጥረት ውስጥ የምትገኘው ግሪክ ለመነጋገር እንደምትፈልግ ገለፀች
17:34 24.07.2025 (የተሻሻለ: 19:04 24.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱከሊቢያ ጋር በባሕር ድንበር ዙርያ ውጥረት ውስጥ የምትገኘው ግሪክ ለመነጋገር እንደምትፈልግ ገለፀች

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ከሊቢያ ጋር በባሕር ድንበር ዙርያ ውጥረት ውስጥ የምትገኘው ግሪክ ለመነጋገር እንደምትፈልግ ገለፀች
አቴንስ የሁለቱን ሀገራት የሜዲትራኒያን ባሕር የጋራ ድንበር ለመወሰን ንግግር እንዲጀምር በትሪፖሊ የሚገኘውን የሊቢያ መንግሥት ጋብዛለች ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ኪሪያኮስ ሚትሶታኪስ ለግሪክ የዜና ማሰራጫ ተናግረዋል።
ጥሪው እ.ኤ.አ 2019 በሊቢያ-ቱርክ የባሕር ድንበር ስምምነት ምክንያት የተፈጠረውን ውጥረት ለመቀነስ ያለመ ነው፡፡ አቴንስ በቱርክ እና በሊቢያ የባሕር ዳርቻዎች መካከል የግሪክ ደሴት ክሬት መገኘቷን ችላ ብሏል በማለት ስምምነቱን በጽኑ ተቃውማ ነበር።
በግንቦት ወር ግሪክ በክሪት አቅራቢያ ለሚደረግ የነዳጅ እና ጋዝ ፍለጋ ጨረታ አውጥታ የነበር ቢሆንም፤ የሊቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አንዳንድ አካባቢዎች አወዛጋቢ በሆኑ ዞኖች ውስጥ እንደሚወድቁ እና የሊቢያን ሉዓላዊ መብቶች እንደሚጥሱ ማሳወቁ ይታወሳል።
ሚትሶታኪስ ግሪክ በትሪፖሊ እና በቤንጋዚ ከሚገኙ የሊቢያ ተፎካካሪ መንግሥታት ጋር እንደምትነጋገር አረጋግጠዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X