የኪዬቭ ባለሥልጣናት ከሞስኮ ጋር ለመስማማት ቅንነት ይጎድላቸዋል ሲሉ የሩሲያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ገለጹ
14:56 24.07.2025 (የተሻሻለ: 15:04 24.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኪዬቭ ባለሥልጣናት ከሞስኮ ጋር ለመስማማት ቅንነት ይጎድላቸዋል ሲሉ የሩሲያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ገለጹ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኪዬቭ ባለሥልጣናት ከሞስኮ ጋር ለመስማማት ቅንነት ይጎድላቸዋል ሲሉ የሩሲያ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ገለጹ
"በቅርብ ጊዜ የዩክሬን ባለሥልጣናት የፈፀሟቸውን ድርጊቶች እና መግለጫዎች ስንገመግም በድርድሩ ከልባቸው እየተሳተፉ አይደለም ለማለት ያስችላናል” ሲሉ ቫለንቲና ማትቪየንኮ ተናግረዋል።
ተጨባጭ ጉዳዮች ላይ በቁም ነገር ተነጋግሮ መሻሻሎች ይኖራሉ ተብሎ ለመጠበቅ ጊዜው ገና ቢሆንም፤ በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል የሚደረገው ድርድር ጠቃሚ በመሆኑ መቀጠል አለበት ሲሉ ባለሥልጣኗ አመልክተዋል።
ሩሲያ ዩናይትድ ስቴትስ የዩክሬን ቀውስ መንስኤዎችን እንድትረዳ እንደምትፈልግና ይህም ጊዜ እና ትዕግስት እንደሚጠይቅ ጨምረው ገልጸዋል።
በተጨማሪም የሞስኮ እና ዋሽንግተን ግንኙነት በዓለም ፖለቲካ አውድ "ሰፊ ገጽታ" ያለው በመሆኑ በዩክሬን ዙሪያ ብቻ ሊያጠነጥን አይገባም ብለዋል ማትቪየንኮ፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X