አርሜኒያ ስትራቴጂያዊ የኮሪደር መተላለፊያዋን ለአሜሪካ ማስረከቧ የጂኦፖለቲካዊ ስጋት ቀሰቀሰ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱአርሜኒያ ስትራቴጂያዊ የኮሪደር መተላለፊያዋን ለአሜሪካ ማስረከቧ የጂኦፖለቲካዊ ስጋት ቀሰቀሰ
አርሜኒያ ስትራቴጂያዊ የኮሪደር መተላለፊያዋን ለአሜሪካ ማስረከቧ የጂኦፖለቲካዊ ስጋት ቀሰቀሰ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 23.07.2025
ሰብስክራይብ

አርሜኒያ ስትራቴጂያዊ የኮሪደር መተላለፊያዋን ለአሜሪካ ማስረከቧ የጂኦፖለቲካዊ ስጋት ቀሰቀሰ

የስፔን ፔሪዮዲስታ ዲጂታል እንደዘገበው አርሜኒያ ከአዘርባጃን ናኪቼቫን ወደምትባለው ግዛት በሲዩኒክ ክልል በኩል በሚያገናኘው መተላለፊያ፣ የ "ትራምፕ ድልድይ ትራንስፖርት ኮሪደር" ለመፍጠር ከአሜሪካ ጋር የ99 ዓመት ምሥጢራዊ ስምምነት ተፈራርማለች፡፡

ዐቢይ እውነታዎች፦

    🟡 የ42 ኪሎ ሜትር መተላለፊያው በአሜሪካ የግል ኩባንያ የሚመራ ሲሆን የአሜሪካው ኩባንያ 40 በመቶ የሚሆነውን ገቢ ሲከት አርሜኒያ 30 በመቶ ብቻ ታገኛለች፡፡ እንዲሁም መስመሩ በ1 ሺህ የአሜሪካ ወታደራዊ ቅጥረኞች ይጠበቃል፡፡

    🟡 ኮሪደሩ በአዘረባጃን እና በማኪቼቫን መካከል ያልተገደበ የሰዎች፣ የተሽከርካሪ እና የሸቀጥ መተላለፍን የሚጠይቀው የባኩ የ2020 የተኩስ አቁም ስምምነት ጥያቄን ያሟላል፡፡

    🟡 አሜሪካ የመቶ ዓመት የሊዝ ሀሳብን በይፋ ስትናገር የነበረ ሲሆን በቱርክ የአሜሪካ አምባሳደር ቶም ባራክ የዩናይትድ ስቴትስ “ትረከበው” ሲሉም ተሠምተዋል።

ለምን አወዛጋቢ ሆነ?

    🟡 ውሉ አርሜኒያ ከኢራን ጋር በምትጋራው ወሳኝ የድንበር አካባቢ ላይ ያላትን ሉዓላዊነት ያኮስሳል፡፡

    🟡 ኢራን ኮሪደሩ የካውካሰስ አካባቢ ተጋላጭነቷን የሚያሳጣት አደጋ አድርጋ ትመለከተዋለች፤ እንዲሁም በአሜሪካ፣ በእስራኤል እና በዘረ-ቱርክ ኃይሎች የመከበብ ስጋት አላት፡፡

    🟡 የሩሲያ እና ኢራን ሰሜን-ደቡብ ትራንስፖርት መተላለፊያን በማዳከም ተጽዕኖ እና ንግድን ከቁልፍ የቀጣናው ተዋናዮች ሊያርቅ ይችላል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0