የኢትዮጵያ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች የትብብር ፎረም በይፋ ተመሠረተ
15:43 21.07.2025 (የተሻሻለ: 15:44 21.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኢትዮጵያ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች የትብብር ፎረም በይፋ ተመሠረተ
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ በይፋ የተመሠረተው ፎረሙ የምርምር ዩኒቨርሲቲዎች በብሔራዊ የልማት፣ ፈጠራና ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት ላይ በጋራ ለመሥራት የሚያስችላቸው መሆኑ ተጠቁሟል።
በፎረሙ የሚካተቱ ተቋማት፦
🟠 በምርምር፣
🟠 በድኅረ ምረቃ ፕሮግራም፣
🟠 በፋኩልቲ ልማት እና
🟠 የፈጠራ ማዕቀፎች ላይ የተሰማሩ እንዲሆኑ ይጠበቃል ነው የተባለው።
ፎረሙ የምርምር ላቦራቶሪዎችና ዲጂታል ፕላትፎርሞችን በጋራ መጠቀምና በእውቀት ሽግግርና በማኅበረሰብ ተኮር ሥራዎች ልምዶችንና አዳዲስ አሠራሮችን መለዋወጥ የሚያስችል መሆኑን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X