የአሜሪካ ቀረጥ ደቡብ አፍሪካ ወደ ብሪክስ ገበያዎች የምታደርገውን ሽግግር ሊያፋጥነው ይችላል ሲሉ ምሁሩ ገለጹ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአሜሪካ ቀረጥ ደቡብ አፍሪካ ወደ ብሪክስ ገበያዎች የምታደርገውን ሽግግር ሊያፋጥነው ይችላል ሲሉ ምሁሩ ገለጹ
የአሜሪካ ቀረጥ ደቡብ አፍሪካ ወደ ብሪክስ ገበያዎች የምታደርገውን ሽግግር ሊያፋጥነው ይችላል ሲሉ ምሁሩ ገለጹ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.07.2025
ሰብስክራይብ

የአሜሪካ ቀረጥ ደቡብ አፍሪካ ወደ ብሪክስ ገበያዎች የምታደርገውን ሽግግር ሊያፋጥነው ይችላል ሲሉ ምሁሩ ገለጹ

ቀረጡ በአሜሪካ ሸማቾች ላይ የዋጋ ጭማሪ ሊያስከትል እና እንደ ማዕድንና ግብርና ባሉ የደቡብ አፍሪካ ቁልፍ የወጪ ንግድ ምርቶች ላይ ያለውን ፍላጎት እንዲቀንስ ያደርጋል ሲሉ የኬፕታውን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስ ተባባሪ ፕሮፌሰር ዝዌሌቱ ጆሎቤ አመልክተዋል።

ጆሎቤ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት ቀረጡ የደቡብ አፍሪካን ምርቶች "ተወዳዳሪነት" በማቀጨጭ የአሜሪካ ገበያ ድርሻቸውን ሊቀንስ ይችላል።

በግብርና እና ማዕድን ዘርፎች የአጭር ጊዜ ሥራ ማጣት ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው፤ የአሜሪካ የወጪ ንግድ አስፈላጊነትን ከልክ በላይ ማጋነን እንዳማያስፈልግ ጠቁመዋል። ለዚህም ተገማች ያልሆነውን ግንኙነት በመጥቀስ፤ አሜሪካ "ብቸኛ" የወጪ ንግድ መዳረሻ እንዳልሆነች አብራርተዋል።

"አማራጩ በመጀመሪያ ደረጃ አዳዲስ ገበያዎችን መፈለግ ነው፤ በሁለተኛ ደረጃ ደግሞ በብሪክስ ውስጥ ባሉ ነባር ገበያዎች ተጨማሪ ዕድሎችን ማግኘት ነው ብዬ አስባለሁ" ብለዋል።

የዩኤስኤአይዲ የገንዘብ ድጋፍ እና የወጪ ንግድ ገቢ መቀነስን በተመለከተ፤ የገቢ ተፅዕኖ ለማቅለል ደቡብ አፍሪካ የማህበራዊ ፕሮግራሞችን በተሻለ ውጤታማነት እና በዝቅተኛ ወጪ ማካሄድ እንደምትችል ተናግረዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0