የሩሲያ ጦር በዩክሬን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ የምሽት ጥቃት ሠነዘረ
15:59 19.07.2025 (የተሻሻለ: 16:04 19.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ ጦር በዩክሬን የመከላከያ ኢንዱስትሪ ተቋማት ላይ የምሽት ጥቃት ሠነዘረ
ፋብሪካዎቹ የሚሳኤሎች እና የጥቃት ድሮኖች ክፍሎችን የሚያመርቱ ናቸው ሲል የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
ሚኒስቴሩ በዩክሬን ወታደራዊ ኦፕሬሽን ዙሪያ ካቀረበው ዕለታዊ ሪፖርት የተወሰዱ ቁልፍ ነጥቦች፦
▪የሩሲያ የአየር መከላከያ ስርዓት ስድስት የአየር ቦምቦችን እና 349 ድሮኖችን መትቶ ጥሏል፣
▪የሩሲያ ጦር በዩክሬን ወታደራዊ አየር ማረፊያ እና የአውሮፕላን ጥገና ማዕከል ላይ ጥቃት ሰንዝሯል፣
▪የዩክሬን ጦር በግምት 1 ሺህ 195 ወታደሮቹን አጥቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X