የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፦ የሕዝብ ድጋፍ እንጂ፤ የውጭ ዶላር ውጤት አይደለም

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፦ የሕዝብ ድጋፍ እንጂ፤ የውጭ ዶላር ውጤት አይደለም
የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፦ የሕዝብ ድጋፍ እንጂ፤ የውጭ ዶላር ውጤት አይደለም - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.07.2025
ሰብስክራይብ

የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ፦ የሕዝብ ድጋፍ እንጂ፤ የውጭ ዶላር ውጤት አይደለም

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስለ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በቅርቡ የሰጡትን አስተያየት ውድቅ ያደረጉት የቀድሞ የኢትዮጵያ ፓርላማ አባልና በሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት ሙሉጌታ ደበበ "ሙሉ በሙሉ በኢትዮጵያውያን የገንዘብ ድጋፍ የተገነባ ግድብ ነው" ብለዋል።

ግድቡ በአሜሪካ የገንዘብ ድጋፍ እንደተደረገለት እና ግብጽ የምታገኘውን ውሃ በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል የሚለውን የትራምፕ ንግግር በተመለከተ ፕሮፌሰሩ አጽንዖት ሰጥተው ሲናገሩ፡-

“ውሃውን መቆጣጠር እና ፍሰቱን ወጥ ያደርገዋል እንጂ...ግብጽም ሆነ ሱዳን በዓባይ ጎርፍ አይጎዱም” ብለዋል።

ሕዳሴ ግድብ ሁሉም ዜጎች፤ “ወጣቱ፣ አዛውንቱ፣ ባለጸጋውና ያጠራቸውም” በአቅማቸው ባደረጉት አስተዋጽኦ የተገነባ የኢትዮጵያ አንድነትና ሉዓላዊነት ምልክት ነው ሲሉ ምሁሩ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡

“አፍሪካውያን እንደ ሕዝብ ሊከበሩ ይገባል” በማለትም ንግግራቸውን አጠናቀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0