የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሃብት ሚኒስትር የሙስና ምርመራ እየተካሄደባቸው ያሉትን የፖሊስ ኃላፊ በመተካት በተጠባባቂነት ተሾሙ
19:32 16.07.2025 (የተሻሻለ: 19:34 16.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሃብት ሚኒስትር የሙስና ምርመራ እየተካሄደባቸው ያሉትን የፖሊስ ኃላፊ በመተካት በተጠባባቂነት ተሾሙ
ሚኒስትሩ ግዌዴ ማንታሼ በነሐሴ ወር ሥልጣናቸውን ለፊሮዝ ካቻሊያ እስኪያስረክቡ ድረስ በዚህ ሚና ያገለግላሉ ሲል የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። ማንታሼ የማዕድንና የነዳጅ ሃብት ሚኒስትርነታቸውንም ይዘው ይቀጥላሉ ተብሏል።
በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ የማንዴላ ኢንስቲትዩትን የሚመሩትና የብሔራዊ የፀረ-ሙስና አማካሪ ምክር ቤት ሰብሳቢ የሆኑት ካቻሊያ ከዩኒቨርሲቲው በጡረታ ከወጡ በኋላ ቦታውን ይረከባሉ።
ሹመቱ የፖሊስ ሚኒስትሩ ሴንዞ ምቹኑ በሙስና፣ ወንጀል በመሸፋፈን እና ምርመራ ላይ ጣልቃ በመግባት ተጠርጥረው ክስ ከተከፈተባቸው በኋላ የመጣ ነው፡፡ ፕሬዝዳንት ራማፎሳ በምርመራው ወቅት የፖሊስ ሥራ "እንደማይስተጓጎል" ቃል ገብተዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X