የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሃብት ሚኒስትር የሙስና ምርመራ እየተካሄደባቸው ያሉትን የፖሊስ ኃላፊ በመተካት በተጠባባቂነት ተሾሙ
19:32 16.07.2025 (የተሻሻለ: 19:34 16.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሃብት ሚኒስትር የሙስና ምርመራ እየተካሄደባቸው ያሉትን የፖሊስ ኃላፊ በመተካት በተጠባባቂነት ተሾሙ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የደቡብ አፍሪካ የማዕድን ሃብት ሚኒስትር የሙስና ምርመራ እየተካሄደባቸው ያሉትን የፖሊስ ኃላፊ በመተካት በተጠባባቂነት ተሾሙ
ሚኒስትሩ ግዌዴ ማንታሼ በነሐሴ ወር ሥልጣናቸውን ለፊሮዝ ካቻሊያ እስኪያስረክቡ ድረስ በዚህ ሚና ያገለግላሉ ሲል የፕሬዝዳንቱ ጽሕፈት ቤት አስታውቋል። ማንታሼ የማዕድንና የነዳጅ ሃብት ሚኒስትርነታቸውንም ይዘው ይቀጥላሉ ተብሏል።
በዊትዋተርስራንድ ዩኒቨርሲቲ የማንዴላ ኢንስቲትዩትን የሚመሩትና የብሔራዊ የፀረ-ሙስና አማካሪ ምክር ቤት ሰብሳቢ የሆኑት ካቻሊያ ከዩኒቨርሲቲው በጡረታ ከወጡ በኋላ ቦታውን ይረከባሉ።
ሹመቱ የፖሊስ ሚኒስትሩ ሴንዞ ምቹኑ በሙስና፣ ወንጀል በመሸፋፈን እና ምርመራ ላይ ጣልቃ በመግባት ተጠርጥረው ክስ ከተከፈተባቸው በኋላ የመጣ ነው፡፡ ፕሬዝዳንት ራማፎሳ በምርመራው ወቅት የፖሊስ ሥራ "እንደማይስተጓጎል" ቃል ገብተዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X