በንግድ ጦርነቶችና ክልላዊ ክፍፍል ምክንያት የኢኮዋስ ዕደገት በ2025 ከ5.1% ወደ 5.0% ይቀንሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለፀ
18:40 16.07.2025 (የተሻሻለ: 18:44 16.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በንግድ ጦርነቶችና ክልላዊ ክፍፍል ምክንያት የኢኮዋስ ዕደገት በ2025 ከ5.1% ወደ 5.0% ይቀንሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገለፀ
ትንበያው በምዕራብ አፍሪካ ሀገራት የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኢኮዋስ) የኢንቨስትመንትና ልማት ባንክ የ2025 የምዕራብ አፍሪካ የልማት ምልከታ ላይ ተዘርዝሯል።
በዕድገት ምልከታው የተጠቀሱ የጠቅላላ የሀገር ውስጥ ምርት ዋና ዋና ተግዳሮቶች፡-
▪ የአሜሪካ ቀረጦች፣
▪ የቡርኪናፋሶ፣ የማሊ እና የኒጀር ከኢኮዋስ መውጣት ንግድ ላይ የፈጠረው መስተጓጎል፣
▪ የሳህል ጥምረት በኢኮዋስ ምርቶች ላይ የሚጥለው የወጪ ንግድ ታክስና ኢኮዋስ ሊወስድ በሚችለው አፀፋዊ እርምጃ የንግድ እንቅስቃሴ መቀነስ፣
▪ በአሜሪካ የሚኖሩ የኢኮዋስ አባል ሀገራት ዜጎች የግብር ጭማሪን ተከትሎ የሚልኩት የገንዘብ መጠን መቀነስ፣
▪ እየጨመረ የመጣው የዋጋ ግሽበት እና የወለድ ምጣኔ።
ℹ ሦስቱ የሳህል ጥምረት ሀገራት በጥር ወር ከኢኮዋስ በይፋ ለቀው ወጥተዋል። ማኅበረሰቡ ውሳኔያቸውን እንዲያስቡበት ቢያሳስብም የጥምረቱ አባላት ከማኅበረሰቡ ለቀው የመውጣት ውሳኔያቸው የመጨረሻ እንደሆነ በተከታታይ አረጋግጠዋል።
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X