ብሔራዊ የንፁህ ምግብ ማብሰያ ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ለ335 ሺህ የሥራ እድል ይፈጠራል ተባለ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱብሔራዊ የንፁህ ምግብ ማብሰያ ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ለ335 ሺህ የሥራ እድል ይፈጠራል ተባለ
ብሔራዊ የንፁህ ምግብ ማብሰያ ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ለ335 ሺህ የሥራ እድል ይፈጠራል ተባለ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 15.07.2025
ሰብስክራይብ

ብሔራዊ የንፁህ ምግብ ማብሰያ ቴክኖሎጂ ፍኖተ ካርታ ለ335 ሺህ የሥራ እድል ይፈጠራል ተባለ

3.8 ቢሊየን ዶላር ፈሰስ የሚደረግበት ሀገራዊ እቅድ 2 ሚሊየን ሴቶችንም ያበቃል ሲል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ በቀጣዮቹ 10 ዓመት ውስጥ የሚተገበረው ብሔራዊ እቅድ ከባሕላዊ ምግብ ማብሰያ (የእንጨትና ኩበት) ወደ ዘመናዊ የምግብ ማብሰያ መፍትሄዎች ለማሸጋገር አልሟል፡፡

በተጨማሪም ፍኖተ ካርታው፦

🟠 በ2035 የንፁህ ምግብ ዝግጅት ተደራሽነትን ከ9 በመቶ ወደ 75 በመቶ ቤተሰቦች ለማሳደግ፣

🟠 በአጠቃላይ 36 ሚሊየን ዘመናዊ ምድጃዎችን በመላ ሀገሪቱ ማሰራጨት፣

🟠 የከተማና የገጠር ነዋሪዎችን የኤሌክትሪክ፣ የፀሐይና የማገዶ ቆጣቢ ምድጃዎች ተጠቃሚ ለማድረግ አቅዷል።

መንግሥት ከጠቅላላ ወጪው 10% ማለትም 380 ሚሊዮን ዶላር ይሸፍናል። ቀሪው ከግል ዘርፍ እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ይጠበቃል ሲል የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0