ፑቲን አስፈላጊ ነው ብለው ካመኑ ትራምፕ በሩሲያ ዙሪያ ባደረጉት ንግግር ላይ አስተያየት ይሰጣሉ ሲል ክሬምሊን ገለፀ
13:36 15.07.2025 (የተሻሻለ: 13:44 15.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ፑቲን አስፈላጊ ነው ብለው ካመኑ ትራምፕ በሩሲያ ዙሪያ ባደረጉት ንግግር ላይ አስተያየት ይሰጣሉ ሲል ክሬምሊን ገለፀ
የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ "የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት መግለጫዎች በጣም አሳሳቢ ናቸው፤ አንዳንዶቹም በግል ፕሬዝዳንት ፑቲንን የተመለከቱ ናቸው" ብለዋል።
በፔስኮቭ የተሰጡ ቁልፍ መግለጫዎች፦
▪ኪዬቭ የአሜሪካ እና የኔቶን ውሳኔ ግጭቱን የመቀጠል ምልክት አድርጋ ቆጥራዋለች፣
▪ዋሽንግተን በሞስኮ እና በኪዬቭ መካከል ውይይቱ እንዲቀጥል ትፈልጋለች፣
▪አውሮፓ ወደ ሰላማዊ መፍትሄ ከመሸጋገር ይልቅ የግጭቱን መካረር ትመርጣለች፣
▪ክሬምሊን ከኪዬቭ ጋር በተደረገው ውይይት የሩሲያ የልዑካን ቡድን ስብጥርን አስመልክቶ የኔቶ ዋና ፀሃፊ ሩተ የሰጡትን አስተያየት ይቃወማል፡፡ የሩሲያ ዋና ተደራዳሪ ሜዲንስኪ ከዩክሬን የልዑካን ቡድን መሪ የላቀ ደረጃ አላቸው።
▪ሩሲያ ከዩክሬን ጋር የሚደረገው ሶስተኛ ዙር ድርድር ጊዜን በተመለከተ እስካሁን ምንም ምልክት አልደረሳትም።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X