በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኦሞ ወንዝ ሙላት ባስከተለው ጎርፍ 81 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለፀ
13:07 15.07.2025 (የተሻሻለ: 13:14 15.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኦሞ ወንዝ ሙላት ባስከተለው ጎርፍ 81 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የኦሞ ወንዝ ሙላት ባስከተለው ጎርፍ 81 ሺህ ሰዎች መፈናቀላቸው ተገለፀ
በክልሉ ደቡብ ኦሞ ዞን ዳሰነች ወረዳ 34 ቀበሌዎች በኦሞ ወንዝ ሙላት ሙሉ በሙሉ እንደተጥለቀለቁ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ምንጮቹን ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
በኦሞ ወንዝ ሙላት የወረዳው ዋና ከተማ የሆነችው ኦሞራቴ ከተማ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በውሃው የመዋጥ ስጋት ውስጥ መግባቷም ነው በዘገባው የተመላከተው።
የኦሞ ወንዝ ሞልቶ የቱርካና ሐይቅ ከኦሞራቴ ከተማ ከዚህ ቀደም ከነበረው 60 ኪ.ሜ ርቀት አልፎ አሁን ላይ ወደ 1.3 ኪ.ሜ ርቀት ላይ መጠጋቱ ምንጮቹ ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X