በሩሲያ ዩኒቨርሲቲዎች በዘላቂ የማዕድን ማውጣት የሠለጠኑ አፍሪካውያን ተማሪዎች ተመረቁ
15:49 12.07.2025 (የተሻሻለ: 16:04 12.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሩሲያ ዩኒቨርሲቲዎች በዘላቂ የማዕድን ማውጣት የሠለጠኑ አፍሪካውያን ተማሪዎች ተመረቁ
ስድስት ታንዛኒያውያን እና አንድ ናሚቢያዊን ጨምሮ ሰባት ተመራቂዎች በእንግሊዝኛ ቋንቋ የማስተርስ ፕሮግራም በማዕድን ጂኦሎጂ ከሩሲያ ሩድን (የሩሲያ ሕዝቦች ወዳጅነት ዩኒቨርሲቲ) እና ከሩሲያ የሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ብሔራዊ ዩኒቨርሲቲ በስኬት ተመርቀዋል።
በሩሲያ የኒውክሌር ኢነርጂ ኮርፖሬሽን ሮሳቶም የሚደገፈው ይህ ፕሮግራም የአፍሪካ ባለሙያዎች የአኅጉሪቱን የበለፀገ የማዕድን ሀብት ለማዘመን እና በዘላቂነት ለማስተዳደር በሚያስፈልጉ ክህሎቶች ለማስታጠቅ ያለመ ነው፡፡
ምሩቃኑ አሁን በሀገራቸው አሸጋጋሪ ለውጥ ለመምራት ተዘጋጅተዋል ያሉት በጄኤስሲ ዩራኒየም ዋን ግሩፕ (የሮሳቶም ንዑስ ድርጅት) የማዕድን ፕሮጀክቶች ዳይሬክተር ኪሪል ኢጎሮቭ-ኪሪሎቭ ናቸው፡፡ የአፍሪካ የማዕድን ቁፋሮ የወደፊት እጣ ፈንታ በሁለቱም ማለትም በቴክኒካል እውቀት እና ኃላፊነት ባለው የሀብት ልማት ቁርጠኝነት ላይ የተመሠረተ መሆኑን አፅንዖት ሰጥተዋል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia
/