ኢትዮጵያ ቪዛቸውን አሳልፈው የሚቆዩ የውጭ ዜጎችን አስጠነቀቀች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮጵያ ቪዛቸውን አሳልፈው የሚቆዩ የውጭ ዜጎችን አስጠነቀቀች
ኢትዮጵያ ቪዛቸውን አሳልፈው የሚቆዩ የውጭ ዜጎችን አስጠነቀቀች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 11.07.2025
ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ ቪዛቸውን አሳልፈው የሚቆዩ የውጭ ዜጎችን አስጠነቀቀች

ማሳሰቢያው አሜሪካ ለኢትዮጵያ፣ ናይጄሪያ እና ካሜሩን ዜጎች የሚሰጠው የቪዛ የቆይታ ጊዜ ወደ ሦስት ወር ማጠሩን ማስታወቋን ተከትሎ የመጣ ነው፡፡

የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነቢያት ጌታቸው የውጭ ዜጎች በተለይም የአሜሪካ ፓስፖርት ለያዙቱ፤ ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ መቆየት በሀገሪቱ ሕግ መሠረት እንደሚያስቀጣቸው አሳስበዋል።

ከዚህ በፊት ኢትዮጵያውያን ዜጎች በተለይም ለንግድ እና ቱሪዝም ወደ አሜሪካ የሚጓዙ አመልካቾች ለሁለት ዓመት የሚቆይ ቪዛ ይሰጣቸው ነበር፡፡ ከሐምሌ 2 ጀምሮ ግን ለ3 ወር የሚቆይ የአንድ ግዜ መግቢያ ቪዛ መስጠት እንደሚጀምር አዲስ አበባ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ማስታወቁ የሚታወስ ነው፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0