የቡና ዘርፉን ለማሳደግ ያለመ ብሔራዊ የቡና ባለድርሻ አካላት አስተባባሪ ኮሚቴ ሥራ ጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየቡና ዘርፉን ለማሳደግ ያለመ ብሔራዊ የቡና ባለድርሻ አካላት አስተባባሪ ኮሚቴ ሥራ ጀመረ
የቡና ዘርፉን ለማሳደግ ያለመ ብሔራዊ የቡና ባለድርሻ አካላት አስተባባሪ ኮሚቴ ሥራ ጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 09.07.2025
ሰብስክራይብ

የቡና ዘርፉን ለማሳደግ ያለመ ብሔራዊ የቡና ባለድርሻ አካላት አስተባባሪ ኮሚቴ ሥራ ጀመረ

ኮሚቴው በህዳር ወር የተዋወቀውን ብሔራዊ የቡና መድረክ ለዘርፉ የወደፊት እድገት የመምራት ኃላፊነት እንደተጣለበት ገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

የኮሚቴው ሰብሰቢ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው የኢትዮጵያ ቡና ዘርፍ ያሉበትን ተግዳሮቶች ዘርዝረዋል፦

🟠 የአየር ንብረት ለውጥ፣

🟠 የገበያ ተጋላጭነት እና

🟠 የቁጥጥር እንቅፋቶች።

የኢትዮጵያ የቡና ዘርፍ 5 ሚሊየን አነስተኛ አርሶ አደሮችን፤ አብዛኞቹ ሴቶችን እንደሚደግፍ እና ሩብ ለሚጠጋ የሀገሪቱ ሕዝብ በቀጥተኛ እና በተዘዋዋሪ መንገድ የሥራ ዕድል እንደፈጠረ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

ኢትዮጵያ በታሪኳ ለመጀመሪያ ግዜ ከቡና የወጪ ንግድ 2.6 ቢሊየን ዶላር ዓመታዊ ገቢ ሰብስባለች።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0