ኢትዮጵያ፣ ኬኒያንና ሶማሊያን የሚያገናኝ አዲስ የፋይበር ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ
20:29 08.07.2025 (የተሻሻለ: 20:44 08.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ፣ ኬኒያንና ሶማሊያን የሚያገናኝ አዲስ የፋይበር ፕሮጀክት ይፋ ተደረገ
የኬኒያ መንግሥት በዲጂታል ትስስር ከኢትዮጵያና ሶማሊያ ጋር ለመገናኘት የሚያስችል፤ በኢሲኦሎ–ማንዴራ ኮሪደር በኩል ከፍተኛ አቅም ያለው የፋይበር ኦፕቲክ ገመድ ለመዘርጋት አቅዷል።
የአፍሪካ ቀንድ መተላለፊያ ልማት የተሰኘውን ፕሮጀክት ዓለም ባንክ በገንዘብ እንደሚደግፈው ቴክ አፍሪካ ኒውስ ዘግቧል።
የኬኒያ መንግሥት ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ የግብዐት ግዢዎችን ለመፈፀም እንዲሁም በአይሲቲ መሠረተ ልማት እና ትስስር ዘርፍ ውስጥ ካሉ የገበያ ባለድርሻዎች ጋር ምክክር ለመጀመር የቅደመ ገበያ ግኑኝነቶችን እያደረገ ነው ተብሏል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X