ብሪክስ ለትብብር እና ተጨባጭ እርምጃ ጊዜው አሁን እንደሆነ "ትክክለኛ መልዕክት" አስተላልፏል ሲሉ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር አስታወቁ
19:54 08.07.2025 (የተሻሻለ: 20:04 08.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ብሪክስ ለትብብር እና ተጨባጭ እርምጃ ጊዜው አሁን እንደሆነ "ትክክለኛ መልዕክት" አስተላልፏል ሲሉ በብራዚል የኢትዮጵያ አምባሳደር አስታወቁ
አምባሳደር ልኡልሰገድ ታደሰ ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ካደረጉት ቃለ-ምልልስ የተወሰዱ ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 መሪዎች ለውጤታማ የዓለም አቀፍ ትብብር ቁርጠኛ እንደሆኑ አረጋግጠዋል፡- “ብሪክስ መፍትሄ ተኮር እንዲሁም የጋራ ተግዳሮቶችን ለመፍታት የሚያስችል የተሻሻለ አጋርነት ነው።"
🟠 ዓለም አቀፍ ስርዓቶችን ለማሻሻል ጠንካራ ጥሪ ተላልፏል፦
የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ሊሻሻል ይገባል፤ “አፍሪካ በትንሹ ሁለት ቋሚ መቀመጫዎችን ማግኘት ይገባታል።"
አሁን ያለው የፋይናንስ መዋቅር “የታዳጊ ሀገሮችን ተገቢ የኢኮኖሚ ፍላጎቶች አያንፀባርቅም።”
🟠 ለአየር ንብረት ለውጥ እርምጃ እና ለአሳታፊ የዲጂታል ስርዓት ተሳትፎ ቃል ገብቷል፦
የአየር ንብረት ለውጥን መዋጋት፤
የ2030 የዘላቂ ልማት አጀንዳን ለማሳካት የዲጂታል ክፍተቶችን ማጥበብ።
🟠 የታዳጊ ሀገራትን ጥቅም የሚያስከብር ሁሉን አቀፍ የሰው ሰራሽ አስተውህሎት አስተዳደር እንዲኖር ግፊት ተደርጓል።
🟠 የጤና ደህንነት ቅድሚያ ተሰጥቶታል፡- “የሁሉም ሰው ደህንነት እሰኪጠበቅ ድረስ የማንም ሰው ደህንነት እርግጥ አይደለም።"
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X