ቱሪዝም ሚኒስቴር ቪዚት ኢትዮጵያ የተሰኘ ዲጅታል መድረክ ይፋ አደረገ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱቱሪዝም ሚኒስቴር ቪዚት ኢትዮጵያ የተሰኘ ዲጅታል መድረክ ይፋ አደረገ
ቱሪዝም ሚኒስቴር ቪዚት ኢትዮጵያ የተሰኘ ዲጅታል መድረክ ይፋ አደረገ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.07.2025
ሰብስክራይብ

ቱሪዝም ሚኒስቴር ቪዚት ኢትዮጵያ የተሰኘ ዲጅታል መድረክ ይፋ አደረገ

ቴክኖሎጂውን ቱሪዝም ሚኒስቴር ከኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ጋር በትብብር እንዳለማው የስፑትኒክ አፍሪካ ዘጋቢ አስታውቋል፡፡

ቪዚት ኢትዮጵያ ፈርጀ-ብዙ ጠቀሜታዎችን የሚያስገኝ የዲጂታል ቴክኖሎጂ ውጤት ሲሆን፦

የቱሪዝም ፀጋዎችን፣ የቱሪስት መዳረሻዎችን፣ የቱሪዝም ምርትና አገልግሎቶችን እንዲሁም የኢትዮጵያን ልዩ የቱሪዝም መገለጫዎች በአንድ ኦንላይን ሥፍራ ለማስተዋወቅ ያስችላል፣

በቱሪዝም እሴት ሰንሰለት ውስጥ የተሠማሩ ቁልፍ የቱሪዝም ተዋንያንን በአንድ ሥፍራ ያገናኛል፣

ጎብኝዎች የኢትዮጵያን የቱሪዝም መስህቦች፣ አገልግሎቶች፣ ምርቶች እና የቱሪስት አገልግሎት ሰጭ ድርጅቶች የተመለከቱ ትክክለኛ እና ፈጣን መረጃዎችን እንዲገኙ ያስችላል፣

ሕጋዊ የቱሪስት አገልግሎት ሰጭ ተቋማትን ከሕገ-ወጦች ለመለየት እና ግልፅና ፍትሐዊ የቱሪዝም ንግድ ለማስፈን ያስችላል፡፡

በአጠቃላይ መድረኩ የኢትዮጵያ ቱሪዝም የዲጅታል ሱቅ/መገበያያ መስኮት ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችል ተዘግቧል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0