የአሜሪካ ኤምባሲ ለናይጄሪያ የተማሪ ቪዛ አመልካቾች የማህበራዊ ትሥሥር ገፅ ፍተሻ እንደሚያካሂድ አስታወቀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአሜሪካ ኤምባሲ ለናይጄሪያ የተማሪ ቪዛ አመልካቾች የማህበራዊ ትሥሥር ገፅ ፍተሻ እንደሚያካሂድ አስታወቀ
የአሜሪካ ኤምባሲ ለናይጄሪያ የተማሪ ቪዛ አመልካቾች የማህበራዊ ትሥሥር ገፅ ፍተሻ እንደሚያካሂድ አስታወቀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 08.07.2025
ሰብስክራይብ

የአሜሪካ ኤምባሲ ለናይጄሪያ የተማሪ ቪዛ አመልካቾች የማህበራዊ ትሥሥር ገፅ ፍተሻ እንደሚያካሂድ አስታወቀ

ኤምባሲው ባወጣው መግለጫ ለ "ኤፍ"፣ "ኤም"፣ "ጄ" የተማሪና የልውውጥ ቪዛ ለማግኘት የሚያመለክቱ ናይጄሪያውያን የማህበራዊ ትሥሥር ገጾቻቸውን "ይፋ" ማድረግ እንዳለባቸው አስታውቋል።

ይህ ፖሊሲ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የተደረገው በሰኔ ወር ሲሆን ወዲያውኑ ተግባራዊ ሆኗል። እንደ ስቴት ዲፓርትመንት ገለጻ ሂደቱ የአሜሪካ ብሔራዊ ደህንነት ጥብቅ የቪዛ ማጣሪያ አካል ነው።

የናይጄሪያ ባለሥልጣናት በዚህ ጉዳይ ላይ እስካሁን አስተያየት አልሰጡም።

በምዕራብ አፍሪካዊቷ ሀገር የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ እ.ኤ.አ ከ2023-2024 ከ20 ሺህ በላይ የናይጄሪያ ተማሪዎች በአሜሪካ ኮሌጆች እና ዩኒቨርሲቲዎች መቀላቀላቸውን ገልጿል። በዚህም ናይጄሪያ በአሜሪካ ውስጥ ካሉ ዓለም አቀፍ ተማሪዎች በቁጥር 7ኛ ደረጃን አግኝታለች።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0