በተባባሰው የኬንያ የሳባ ሳባ ተቃውሞ ቢያንስ 4 ሰዎች በተኩስ መገደላቸው ተዘገበ
16:59 07.07.2025 (የተሻሻለ: 17:24 07.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በተባባሰው የኬንያ የሳባ ሳባ ተቃውሞ ቢያንስ 4 ሰዎች በተኩስ መገደላቸው ተዘገበ
ሁለቱ ሰዎች በናይሮቢ ካንጌሚ ቀጣና ቀሪዎቹ ደግሞ በመዲናዋ ደቡብ ምዕራብ ንጎንግ መገደላቸውን የሀገሪቱ የዜና ጣቢያዎች በቀጥታ ስርጭት ዘግበዋል፡፡
የካንጌሚ አንዱ ሟች ተቃውሞ ላይ እንዳልነበረና ከሥራ ወደ ቤቱ እየሄድ እያለ በተባራሪ ጥይት መገደሉን የዐይን እማኞች ለዜና ጣቢያው ተናግረዋል፡፡
አድማ በታኝ ፖሊሶች ሰልፈኛውን ለመቆጣጠር ሲሞክሩ በበርካታ የኬንያ ከተሞች ተኩሶች ተደምጠዋል፡፡ ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ እየተኮሰ ነው፡፡
ዓመታዊው የሳባ ሳባ ተቃውሞ በኬንያ የአንድ ፓርቲ አገዛዝ እንዲያበቃ ያደረገውን የ1990 ንቅናቄ ይዘክራል፡፡ የዘንድሮ ተቃውሞ የኑሮ ውድነት፣ ሙስና እና ፖሊስ ከሰሞኑ የወሰደው አስቃቂ እርምጃ ያፋፋመው ነው፡፡
የማኅበራዊ ሚዲያ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X
© telegram sputnik_ethiopia
/ © telegram sputnik_ethiopia
/ 
© telegram sputnik_ethiopia
/