አሜሪካ ከኪዬቭ እየራቀች መምጣቷን ተክትሎ፤ ብላክሮክ የዩክሬን ማገገሚያ ፈንድን አቋረጠ
20:07 05.07.2025 (የተሻሻለ: 20:24 05.07.2025)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ ከኪዬቭ እየራቀች መምጣቷን ተክትሎ፤ ብላክሮክ የዩክሬን ማገገሚያ ፈንድን አቋረጠ
ግዙፉ የአሜሪካ ኢንቨስትመንት ኩባንያ ብላክሮክ፤ ፈንዱ ላይ ኢንቨስት ለማድረግ ፍላጎት ያላቸው ባለሃብቶች በማጣቱ የወሠደው ውሳኔ እንደሆነ የአሜሪካ ሚዲያ ዘግቧል።
ገንዘብ ማሰባሰቢያው በሚቀጥለው ሳምንት በሮም በሚካሄደው የዩክሬን የመልሶ ግንባታ ጉባኤ ላይ ይጀመራል ተብሎ ታቅዶ ነበር። እ.ኤ.አ. መጋቢት 2024 የምዕራባውያን ባንኮች እና የግል ባለሀብቶች እስከ 15 ቢሊየን ዶላር የተገመተ ገንዘብ ወደ ንቅናቄው ፈሰስ ለማድረግ አቅደው እንደነበር ሚዲያው አስታውሷል።
ከአሜሪካ ውጭ የሚደረግ የቱም ዓይነት አዲስ እቅድ ውጤታማነቱ ግልጽ ባይሆንም፤ ፈረንሳይ ግን ብላክሮክ የሠረዘውን ፈንድ የሚተካ ፕሮፖዛል እያዘጋጀች ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X