ታንዛኒያ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች አስገዳጅ የ44 ዶላር የጉዞ ዋስትና ይፋ አደረገች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱታንዛኒያ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች አስገዳጅ የ44 ዶላር የጉዞ ዋስትና ይፋ አደረገች
ታንዛኒያ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች አስገዳጅ የ44 ዶላር የጉዞ ዋስትና ይፋ አደረገች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 05.07.2025
ሰብስክራይብ

ታንዛኒያ ለውጭ ሀገር ጎብኚዎች አስገዳጅ የ44 ዶላር የጉዞ ዋስትና ይፋ አደረገች

እንደ ሃገሪቱ የገንዘብ ሚኒስቴር፤ የጉዞ ኢንሹራንስ ክፍያው (በሀገር ውስጥ ምንዛሬ የሚከፈል)፤ ታንዛኒያ የተጓዦችን ጥበቃ በማጠናከር ራሷን የምስራቅ አፍሪካ ቀዳሚ መዳረሻነት ለማስቀመጥ ያለመ መሆኑን አስታውቋል።

የዋስትና ክፍያው የሚከተሉትን ያጠቃልላል፦

የአደጋ ጊዜ ሕክምና፣

የጠፋ ሻንጣ ካሳ፣

ለአደጋ መታደጊይስ አገልግሎቶች፣

ወደ ሀገር ቤት የመመለሻ ወጪዎች።

ትግበራው በመንግሥት ጋዜጣ ታተሞ የሚወጣ የቁጥጥር መመሪያዎችን ይጠብቃል። ከመቼ እንደሚጀምር ገና አልተረጋገጠም፡፡

የምስራቅ አፍሪካ ማኅበረሰብ እና የደቡብ አፍሪካ ልማት ማኅበረሰብ አባል ሀገራት ዜጎች አዲሱ የዋስትና መስፈርት አይመለከታቸውም።

ፖሊሲው የዛንዚባርን የ2024 የኢንሹራንስ ሞዴል የተከተለ ነው። የቱሪዝም ባለሙያዎች ግን ታንዛኒያን ረግጠው ወደ ዛንዚባር የሚጓዙ ጎብኚዎችን እጥፍ የማስከፈል ስጋት እንዳለ በማንሳት፤ የታንዛኒያን የተዋሃደ የቱሪዝም ብራንድ ሊጎዳ ይችላል የሚል ስጋታቸውን ገልፀዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0