የመከላከያ ምርምር እና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ የሰው ሰራሽ አስተውህሎትን ሊያዋህድ እንደሚገባ ተገለፀ
14:11 05.07.2025 (የተሻሻለ: 14:34 05.07.2025)
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየመከላከያ ምርምር እና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ የሰው ሰራሽ አስተውህሎትን ሊያዋህድ እንደሚገባ ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የመከላከያ ምርምር እና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ የሰው ሰራሽ አስተውህሎትን ሊያዋህድ እንደሚገባ ተገለፀ
የሳይበር ጦርነት አዝማሚዎችን ታሳቢ በማድረግ የቴክኖሎጂ የውጊያ አውዶችን ማየት እንደሚኖርበት ነው የመከላከያ ሠራዊት የትምህርትና ሥልጠና ኃላፊ ሌተናል ጄኔራል ይመር መኮንን አጽንኦት የሰጡት።
ሌተናል ጄኔራል ይመር ረቂቅ ፖሊሲው የኢትዮጵያን የመከላከል አቅም ለማሳደግና ሠራዊቱ የሚፈጠሩ የጸጥታ ችግሮችን ለመቅረፍ የተሻለ ዝግጅት ለማድረግ የላቀ ጠቀሜታ አለው ብለዋል።
የመከላከደ ዋር ኮሌጅ ዋና አዛዥ ብርጋዴር ጄኔራል ቡልቲ ታደሰ የመከላከያ ሠራዊትን ሁለንተናዊ ለውጥ በስኬት መምራት የሚያስችሉ ጥናትና ምርምር ልማት ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልጸዋል።
በመከላከያ ሚኒስቴር የኢፌዴሪ ዋር ኮሌጅ የብሔራዊ ደኅንነት ኮንፍረንስ፣ የምርምርና ልማት ረቂቅ ፖሊሲ ላይ ዋና የዘርፉ ተዋናዮች የተሳተፉበት የውይይት መደረጉን የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X